ሰላማዊት 29 አመቷ ነው። የመጀመሪያ ልጇን ኤርትራ ውስጥ ወለደች። እሷና ቤተሰቧ እዚያ በጣም ስለተቸገሩ ወደ ጣሊያን ለመሄድ ወሰኑ።
ኢንጋ ገና 19 ዓመት ሳይሞላት በፊት ከቤት ወጣች። ወደ ኖርዌይ ሄዳ የመጀመሪያ ልጇን እዚያ ወለደች።
ሰላማዊት ሁለተኛ ልጇን ባረገዘች ጊዜ ሌላ ሀገር ልጅ መውለድ ምን ሊመስል እንደሚችል አሠበች።
ሰላማዊት እና ኢንጋ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ ናቸው። ሰላማዊት የመውለድ ልምድ ስላላት ደህንነት ተሰምቷታል። ኢንጋ ስለ መውለድ እናቷን ኣናገረች።
ሁለቱም ሴቶች በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገሮች ነፍሰ ጡር እናቶች የቅድመ ወሊድ እንክብካቤ የማግኘት መብት እንዳላቸው ሰምተው ነበር። ይህ ማለት በእርግዝና ወቅት እርዳታ ያገኛሉ ማለት ነው። ሰላማዊት መፀነሷን እንዳወቀች ከዶክተሯ ጋር ቀጠሮ ያዘች። የሰላማዊት ባል በመኪና ወደ ሐኪም ወሰዳት።
ሐኪሙ አንዳንድ ምርመራዎችን ካደረገ በኋላ ሰላማዊት አንዳንድ ነፍሰ ጡር እናቶች የሚይዘው የስኳር በሽታ እንዳለባት አወቀ። ጤናማ ምግብ መመገብ እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ነበረባት። ሰላማዊት እሷና ልጇ ከመታመማቸው በፊት ዶክተር ጋር ቀድማ በመሄዷ ተደሰተች።
የኢንጋ ጎረቤት ልጅ ለመውለድ እየሞከረች እንደሆነ ስትሰማ ጎረቤቷ እንዳረገዘች ዶክተር እንድትሄድ በፍጥነት ነገሩዋት። በዚህ መንገድ እሷ እና ልጇ ጤናማ መሆናቸውን ማረጋገጥ ትችላለች። ዶክተሩ ለነፍሰ ጡር ሴቶች ጠቃሚ የሆነውን ፎሊክ አሲድ የተባለውን ቫይታሚን እንድትወስድ ነገራት።
ኢንጋ እና ሀኪሟ በእርግዝናዋ ወቅት መደበኛ ምርመራ ለማድረግ አዋላጅ ነርስ እንድታገኝ ተስማሙ። አዋላጇ ስለ ምግብ እና እረፍት እንዲሁም እራሷን እና ልጇን እንዴት ደህንነት እና ጤንነቷን መጠበቅ እንዳለባት መረጃ ሰጣት።
ሁለቱም ሴቶች ጤናማ ልጆችን ወለዱ። ሰላማዊት ሌላ ወንድ ልጅ ወለደች። ኢንጋ ደሞ ሴት ልጅ ወለደች። ባሎቻቸው በጣም ኩሩ ነበሩ፣ እናም ለሚያውቋቸው ሁሉ ስለ ጠንካራ ሚስቶቻቸው እና ጤናማ ልጆቻቸው ያወሩ ነበር።