ስሜ ማሊክ ይባላል 39 አመቴ ነው። የተወለድኩት አፍጋኒስታን ነው። የኔ ሃይማኖት ከአፍጋኒስታን ዋና ሃይማኖት የተለየ ነው።
My name is Malik and I am 39 years old. I was born in Afghanistan. My religion is different from the main religion in Afghanistan.
ለብዙ ዓመታት የእኔ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ ሰዎች ስደት ደርሶባቸዋል። ይህ ለቤተሰቤ በጣም ከባድ ነበር።
For many years, people who belong to my religion have been persecuted. This has been very difficult for my family.
ከጥቂት አመታት በፊት ጦርነት ነበር። እኔም እንዳልገደል ፈራሁ። ቤተሰቤን ትቼ ወጣው አውሮፓ ለመሄድ እና ኣዲስ ህይወት ለመጀመር።
A few years ago there was a war. I was afraid I would be killed. I left my family to go to Europe and start a new life.
ለብዙ ኪሎ ሜትሮች በእግር ተጓዝኩ። አንዳንድ ጊዜ ምንም ምግብ አልነበረኝም እናም የማርፍበት ቦታ አልነበረኝም። አብሬያቸው የተጓዝኳቸው አንዳንድ ሰዎች ሞተዋል።
I walked for many kilometres. Sometimes I had no food and nowhere to stay. Some of the people I travelled with died.
በመጨረሻ ደረስኩ። የረዱኝ አንዳንድ የሀገሬ ሰዎች አገኘሁ። ያለ እነርሱ ምን እንደማደርግ ኣላውቅም ነበር።
Finally I arrived. I met some people from my own country who helped me. I do not know what I would have done without them.
ቋንቋውን መማር ጀመርኩ ግን ከባድ ነበር። ሥራ ለማግኘት ቋንቋውን መናገር አስፈላጊ እንደሆነ አውቃለሁ።
I started to learn the language, but it was hard. I knew that speaking the language was important to get a job.
መጀመሪያ ላይ ቋንቋውን ለመማር ለበርካታ ዓመታት አጠናሁ። ከባድ ነበር ነገር ግን አዳዲስ ነገሮችን መማር ያስደስተኛል።
I studied for several years, at first to learn the language. It was hard, but I enjoy learning new things.
ካጠናሁ በኋላ መሥራት ጀመርኩ። መጀመሪያ ሬስቶራንት ውስጥ ሰራሁ። ከዛ ሌሎችን መርዳት ስለምፈልግ አስተማሪ ሆንኩ።
After studying I started working. First I worked in a restaurant, and then I became a teacher because I want to help others.
አንድ ቀን ወደ አፍጋኒስታን ለመመለስ ተስፋ አደርጋለሁ። እዚያ ያሉ ብዙ ሰዎች እርዳታ ይፈልጋሉ። እና እነርሱን መርዳት እፈልጋለሁ።
I hope to go back to Afghanistan one day. Many people there need help, and I want to help them.